በሀገራችን የሙዚቃ ዘርፍ ውስጥ ከ 50 ዓመታት በላይ የቆየው የክብር ዶ/ር አርቲስት ማሕሙድ አህመድ የመድረክ ስንብት የመጨረሻ ኮንሰርቱን ሊያቀርብ ነው ።
የትዝታው ንጉስ ማህሙድ አህመድ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ ላበረከተው አስተዋፅኦ ክብር ይገባዋል በማለት አድናቂዎቹ እና ወዳጆቹ ኮሚቴ በማዋቀር የጋሽ ማህሙድን የመጨረሻ የመድረክ መሰናበቻ ኮንሰርት ማዘጋጀት ፣ በሕይወት ታሪኩ ላያ ያተኮረ መፅሀፍ ማስመረቅ ፣ በስሙ መንገድ ለማሰየምና ሀውልት ለማቆም ላለፉት ሁለት አመታት ሲሰሩበት እንደቆዩ በሸራተን አዲስ ሆቴል በሰጡት መግለጫ ተገልጿል።
በመሆኑም የመጨረሻ የመድረክ ስንብት የሙዚቃ ድግስ ፣ የጋሽ ማህሙድን ሕይወት የሚዘክር መፅሀፍ ምርቃት ጥር 03/ 2017 ዓ.ም በሚኒሊየም አዳራሽ ይካሔዳል።
ለሀገራችን የሙዚቃ ዘርፍ ማደግ ከፍተኛ አስቸዋፅኦ ያበረከተውን የክቡር ዶ/ር አርቲስት ማህሙድ አህመድ ማመስገኛና ማክበሪያ መድረክ ላይ ሁሉም ሰው በመታደም በክብር እንዲሸኘው የድግሱ አዘጋጅ ጆርካ ኤቨንት ጥሪ አቅርቧል።