የኢትዮጵያ ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአጀንዳ ማሰባሰብ መርሓ-ግብር በደ/ም/ኢ/ህ/ ክልል ማካሄድ ጀምሯል።
ዛሬ እሁድ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ተከታታይ ቀናት የሚካሄደው አጀንዳ ማሰባሰብና የተወካዮች መረጣ ከክልሉ 57 ወረዳዎች የተውጣጡ ተወካዮች ተሳታፊ ሁነዋል።
የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዘገዬ አስፋው ሃገሪቱ የልዩነት ቀውስ ውስጥ፣ የፖለቲካ አለመግባባት፣ ጦርነት ውስጥ በመሆኑ ሃራዊ ምክክሩ አስፈልጓል በማለት ለተሳታፊዎች አስረድተዋል።
ምከትል ኮሚሽነር አቶ ሙሉጌታ አጎ በአገሪቱ እንዳንድ አካባቢዎች በሃሳብ ከመግባባትና መነጋገር ይልቅ የሃይል አማራጮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ጠቅሰው ተሳታፊዎች ሃገራዊ ፋይዳ ያላቸውንና መሰረታዊ የሆኑ የህዝብ አጀንዳዎችን እንዲያነሱ ጠይቀዋል።
ከዛሬ ጀምሮ በመካሄድ ላይ ባለው መርሃግብር ከአጀንዳ ማሰባሰብ በተጨማሪ በሃገራ ምክክር ላይ የሚሳተፉ ተወካዮች የሚመረጡበት ነው።
ሀገሬ ቴሌቪዥን ተጨማሪ መረጃዎችን ከደ/ም/ኢ/ህ ክልል ቦንጋ ከተማ ማድረሷን ትቀጥላለች።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *